
የጤና ባለሙያዎች የመውጫ እና የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት
በትምህርት ሚኒስቴር እና በጤና ሚኒስቴር በጋራ ሰኔ 19/2016 ዓ.ም የተሰጠው የጤና ባለሙያዎች የመውጫ እና ብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
ተመዛኞች ከዛሬ ነሐሴ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።
በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል regulatory.moh@moh.gov.et ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ዲግሪ የያዛችሁ እና የጤና ሚኒስቴርን የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች ከነሐሴ 03/2016 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ለክልል የጤና ተቆጣጣሪ አካላት ይላካል ተብሏል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህን ተከትሎ በሚወጣ ማስታወቂያ የተግባር ምዘና (OSCE) ፈተና የምዝገባ መርሐግብር ስለሚወጣ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሚኒስቴሩ ጠይቋል።
????Share share????
????????ለተጨማሪ መረጃ????????
https://t.me/Temhert_Minister1
https://t.me/Temhert_Minister1
https://t.me/Temhert_Minister1